ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Thursday, May 3, 2012

የግንቦት ልደታ የንግሥ ሥነ-ሥርዓት በኦፕፊኮን ደብረ ገነት ቅ.ማርያም ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል!

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

በዙሪክ/ኦፕፊኮን (ስዊዘርላንድ)የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የዘንድሮውን የግንቦት ልደታን የምታከብረው ዕሑድ ሚያዝያ 28 ቀን 2004 ዓ.ም.(06.05.2012) ነው::

እንደተለመደው ሁሉ ለበዓሉ ተስማሚ በሆኑ ያሬዳዊ ዜማዎች: ቅዳሴና ንግሥ የሚከበር ሲሆን ከቅዳሴ በኋላ የእመቤታችንን ልደት ለማስታወስ ጸበል ጸዲቅ ለየት ባለ መልኩ መናፈሻ ውስጥ የሚደረግ መሆኑን የመስተንግዶ ክፍሉ አስታውቋል::

በስዊዘርላንድና አካባቢው ነዋሪ የሆኑ የተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ በዚህ እለተ ሰንበት በመገኝት የበረከቱ ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱ ጥሪዋን ታቀርባለች::

No comments:

Post a Comment