Friday, January 20, 2012
Piniel - New Ethiopian Orthodox Tewahedo Christian Mezmur CD by our very own Zemari Tilahun Abshir
የዘማሪ ጥላሁን አብሽር አዲስ መንፈሳዊ መዝሙር
በስዊዘርላንድ የዙሪክ/ ኦፕፊኮን ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ማሰርያ/መግዣ ይውል ዘንድ የቀረበ! ሲዲውን በመግዛት ቤተ ክርስቲያናችንን ይታደጉ:: ሲዲውን ለመግዛት መካነ ድራችንን ይጎብኙ: ወይም በመልዕክት ማሕደራችን :ethiopian_orthodox@yahoo.de የማዘዣ ቅጽና ዝርዝር መመርያ ያግኙ::
| አቀባበል: |
Thursday, January 12, 2012
የአንድ ምእመን ሮሮ
የአንድ ምእመን ሮሮ (ከዲያቆን ዳንኤል ክብረት ጦማር የተወሰደ)
(አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትምህርት ይሰጣል፡፡ እኒህ ምእመን ቁጭ ብለው ይሰማሉ፡፡ የሰባኪው ሁኔታ አልጣማቸውምና በልባቸው እንዲህ ያማርራሉ፡፡)
«ምን ገባችሁ ገባችሁ ይላል፤ ይልቅ እንዲገባን አድርጎ አያስተምረንም፡፡ አሁን ኢየሱስ ከናዝሬት ወደ ገሊላ ሄደ ብሎ እልል በሉ ማለት ምን ማለት ነው፡፡ አሁን እኛ እልል የምንለው ገሊላ ስለ ሄደ ነው፤ ከናዝሬት ስለተነሣ ነው? ወይስ ስለሄደ ነው? እና ላይሄድ ኖሯል፡፡ ለምን ሄደ? እንዴት ሄደ? ሄዶ ምን አገኘን እያለ እንዲነግረን እንጂ ወደ ገሊላ መሄድማ እማሆይ አማረችስ ባለፈው ጊዜ ኢዬሩሳሌምን ሲሳለሙ ገሊላ ሄደው አልነበረም? ወይ አንተ ፈጣሪ፡፡
ልሂድ ልውረድ ልጄንም ላምጣው፣ እያሉ በርእስ መቀለድ ምን የሚሉት አባዜ ነው፡፡ ሰሞኑንማ የእብራይስጥ ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ፈልጋችሁ ያንን ርእስ ካላደረጋችሁ ትታሠራላችሁ የተባላችሁ ነው የምትመስሉት፡፡
አምሳ ዳቦ ከመላስ አንደ ዳቦ መቅመስ አሉ፡፡ አሁን ይህንን ሁሉ ጥቅስ ከመዘርገፍ አንዱን ትንትን አድርጎ ቢያስተምረን አይሻልም፡፡ ስንት ሕፃናት አሉ፡፡ አረጋውያን አሉ፡፡ መጻፍ የማይችሉ አሉ፡፡ ምን ያደርጉታል አሁን፡፡ «ቀላል አይደለንም» ለማለት ካልሆነ በቀር፡፡እኔ የምለው የስብከት ዓላማው ማስተማር መሆኑ ቀርቶ ማዝናናት ሆነ እንዴ፡፡ እነ ክበበው ገዳ ምን ሠርተው ሊበሉ ነው እንዲህ አገልጋዩ ሁሉ ቀልደኛ ከሆነ፡፡ ቅዳሴ ቢያልቅበት ቀረርቶ ሞላበት አሉ እማሆይ አማረች፡፡ ቆይ አሁን ምን አድርጉ ነው የሚሉን? ኑ ተባልን መጣን፤ አዋጡ ተባልን አዋጣን፤ ጹሙ ተባልን ጾምን፣ ጸልዩ ተባልን ጸለይን፣ ገዳም ሂዱ ተባልን ደርሰን መጣን፣ መጻፍ ግዙ አሉን ገዛን፣ ካሴት ግዙ አሉን ገዛን፣ እልል በሉ ተባልን አልን፣ አጨብጭቡ ተባልን አጨበጨብን፣ አሁንም ይመጡና ኃጢአታ ችሁ ነው ይህንን ሁሉ መዓት ያመጣው ይሉናል፡፡ እሺ ደግሞ ምን ቀረን?አሁን ማን ይሙት ችግር ያለው ከኛ ነው ከእናንተ፡፡ የጥንት ሰዎች ዕድለኞች ሳይሆኑ አልቀሩም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሄደው ገድል እና ተአምር ሰምተው ነበር የሚመጡት፡፡ እኛ በናንተ ምክንያት ጭቅጭቅ እና ንትርክ ሆነኮ የምንሰማው፡፡ ስለ ጊዮርጊስ እና ተክለ ሃይማኖት፣ ስለ ጳውሎስ እና ጴጥሮስ፣ ስለ ክርስቶስ ሠምራ እና መስቀል ክብራ መስማት ትተን ስለ ሰባኪ እገሌ እና ሰባኪ እገሌ፣ ስለ እገሌ ቡድን እና እገሌ ቡድን ሆነኮ የምንሰማው፡፡ አይ ስምንተኛው ሺ፡፡
ስምንተኛው ሺ ቢሆን ነው እንጂ የማይጾሙ የሚጾሙትን፣ የማያስቀድሱ የሚያስቀድሱትን፣ የማይፋቀሩ የሚፋቀሩትን፣ ያልጸኑት የጸኑትን፣ የማይቆርቡ የሚቆርቡትን፣ ዓለምን ያልተው ዓለምን የተውትን፣ ያላመኑ ያመኑትን የሚያስተምሩት፤ ሌላ ምን ቢሆን ነው?
አሁን የት እንሂድ? ከዓለም ወደዚህ መጣን፤ ከዘህ ደግሞ ወዴት እንሂድ፡፡ እንዴው ለመሆኑ ስለ ፓትርያርክ፣ ስለ ጳጳስ፣ ስለ ሲኖዶስ፣ ስለ ካህን፣ ስለ ዲያቆን፣ ስለ ባሕታዊ፣ ስለ መነኩሴ፣ ስለ ሰባኪ ደግ ነገር የምንሰማበት ዘመን ይመጣ ይሆን፡፡ ስለ ገዳማት የምንሰማው ሁሉ ተራቡ፣ ተቸገሩ፣ አበምኔቱ ተማሪዎችን አባረሩ፣ መነኮሳቱ አበ ምኔቱን አባረሩ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው ገድል ተጋድለው ተአምር አደረጉ የሚል የምንሰማው፡፡ስለ ጳጳሳት የምንሰማው በራቸው ተደበደበ፣ በሑዳዴ ጾም ከበሮ አስመቱ፣ በሰው ሀገረ ስብከት ገብተው አተራመሱ፣ ቤት ገዙ፣ መኪና ገዙ፣ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው እንደነ ዮሐንስ አፈወርቅ ለእውነት ተጋደሉ የሚል ወሬ የምንሰማው፡፡ ስለ ፓትርያርክ የምንሰማው እገሊት ትመራቸዋለች፣ ሐውልት ሠሩ፣ ውጭ ሀገር ሄደው ተዝናኑ፣ ገንዘብ አባከኑ፣ በዘመድ ሠሩ፣ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው እንደ አትናቴዎስ ለሃይማ ኖታቸው መሥዋዕትነት ከፈሉ፣ እንደ ድሜጥሮስ ተአምር አደረጉ የሚል የምንሰማው፡፡ አልታደልንም መሰል፡፡የጥንት ሰዎች በየ ደብሩ ሊቃውንቱ ምሥጢር እና ቅኔ ሲዘርፉ ነበር አልነበር እንዴ ያሉን፡፡ ምነው በኛ ዘመን ቅኔው ቀርቶ ሙዳየ ምጽዋት ብቻ ሆነ የሚዘረፈው፡፡ በየትምህርቱ ስንሰማ ታሥረው በግንድ፣ ተይዘው በግድ ተሾሙ አይደል እንዴ የምትሉን፡፡ ይኼ የነገራችሁን ነገር ተረት ቢሆን ነው እንጂ እንዴት በኛ ዘመን ሊለወጥ ቻለ ታድያ፡፡አንዳንዴኮ እዚያው ተአምረ ማርያማችንን ብቻ እየሰማን፣ ከግብጽ በሚመጣ አንድ ጳጳስ እየተባረክን ውስጡን ሳናውቀው በቀረን ኖሮ ያሰኛል፡፡ እንዴው እነዚህ ሐዋርያት የሚባሉ ይህንን መጽሐፍ የጻፉት በምን ቀን ነው? የአባቶቻችን ተረት እንኳን ለዛ ነበረው፡፡ ማቴዎስ እንዲህ አለ፤ ሉቃስ ይህንን አለ፡፡ ጳውሎስ እንዲህ አለ፡፡ እሺ አለ፡፡ ደግሞኮ «አያችሁ» ይለናል፡፡ ምኑን ነው የምናየው፡፡ እግዚአብሔርንማ እንዳናየው አንተው ራስህ ጋርደህን፡፡ ምን አስተማረ? መባሉ ቀርቶ ማን አስተማረ ሆነ፡፡ ስንት ሰው ተለወጠ? መሆኑ ቀርቶ ስንት ሰው ተሰበሰበ ሆነ፡፡ እኛ የዚህን ዓለም የአለባበሰ ፋሽን እንድንተው አስተማራችሁን፡፡ እሺ ብለን ትተን ስንመጣ እናንተ የየቀሚሱን ዓይነት ፋሽን አመጣችሁት፡፡ ምንድን ነው ይኼ ሁሉ አሸንክታብ? እናንተ መድረክ ላይ ገዝፋችሁ እየታያችሁ ጌታን በየት እንየው፡፡ የሚነገረው ስለ እናንተ ነው፡፡ «ጸጋ የበዛለት፣ታዋቂ፣ ልዩ፣ ልብ ሰባሪ፣አጥንት ነቅናቂ» ከበሮ ለምን ይጮኻል ቢሉ ውስጡ ባዶ ስለሆነ ነው አሉ አሉ፡፡ ተግባራችሁ ይነግረናልኮ፣ ብዙ ማስታወቂያ አያስፈልግም፡፡ እናንተ ስለ እግዚአብሔር ተናገሩ፣ እርሱ ስለ እናንተ ይናገራል፡፡ እናንተ ስለ ራሳችሁ ስለምትናገሩ ግን እርሱን ዝም አሰኛችሁት፡፡እንዲያውም ብዙ ሕዝብ ከሌለ አንመጣም ትላላችሁ አሉ፡፡ ለመሆኑ ይኼ እናንተ የያዛችሁት መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ አንዲት ሳምራዊትን ሴት ለብቻዋ ማስተማሩን አይናገርም ይሆን፡፡ ለመሆኑ ስብከት ለእናንተ ሥራ ነው ወይስ አገልግሎት? ይህንን ሕዝብ ምን እናቅርብለት ብላችሁ ትጨነቃላችሁ? ትጸልያላችሁ፣ ታነባላችሁ? ትጠይቃላችሁ? ወይስ? ምናልባት የማትኖሩበትን ስለምታስ ተምሩን ይሆን መለወጥ ያቃተን? የሌላችሁን ስለምትለግሱን ይሆን ብዛት እንጂ ጥራት ሊኖረን ያልቻለው? ክርስቲያን ታደርጉናላችሁ ብለን ብንመጣ ቲፎዞ አደረጋችሁን፡፡ ለቲፎዞ ለቲፎዞማ አርሴናልና ማንቸስተር ነበሩልንኮ፡፡ ሲገባባቸው ተናደን ሲያገቡ ጨፍረን ቤታችን እንገባ ነበር፡፡ አሁንምኮ እንደዚያ አደረጋችሁት ሁሉም ቲፎዞ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ የእገሌ ተከታይ ይባልልኛል፡፡ አስከትላችሁ አስከትላችሁ የት ታደርሱን ይሆን?የታደሉት የዮሐንስ መጥምቅ ተከታዮች መጨረሻቸው ከክርስቶስ ጋር መገናኘት ሆነ፡፡ እኔ ዝቅ ዝቅ ልል እርሱ ግን ከፍ ከፍ ሊል ይገባዋል ብሎ አገናኛቸው፡፡ የርሱ ሥራ ድልድይ መሆን ነበረ፡፡ እኛ የናንተ ተከታዮችስ ታገናኙን ይሆን? ቆይ ግን የሚያስፈልገንን ነው የምትነግሩን ወይስ የምትፈልጉትን? ልታሳውቁን ነው የምትመጡት ወይስ ማወቃችሁን ልትነግሩን፡፡ የምታስተምሩትንስ ታውቁታላችሁ ወይስ ታምኑበታላችሁ?
ቢቻል የምትታዩ ከዋክብት ሁኑልን፣ ባይቻል ደግሞ የማትታዩ ከዋክብት ሁኑ፡፡ ቢቻል አርአያችሁን ምሳሌያችሁን እንድንከተል የምትነግሩንን ብትኖሩት፣ የምታስተምሩትን በእናንተ ብናየው፤ ባይቻል ደግሞ የማታስተምሩንን በእናንተ እንዳናየው ብታደርጉ፡፡
እንዴው ግን እዚህ መሬት ስንቀመጥ የማናውቅ እንመስላችኋለን? እዚህ ቦታኮ በእድሜም በዕውቀትም የምንበልጣችሁ ሰዎች አለን፡፡ አጋጣሚውኮ ነው እናንተን ለመድረክ እኛን ለአግዳሚ ወንበር የዳረገን፡፡ ምናልባትም አንዳንዶቻችን በትኅትና ምክንያት እንጂ ርእሱን ስትናገሩ እንደ ነጣቂ ባለ ቅኔ መደምደሚያችሁንም እናውቀዋለንኮ፡፡ እኛኮ እየተማርን ያለነው ቃለ እግዚአብሔር ምግብ ስለሆነ ነው፡፡ ቃለ እግዚአብሔርኮ ዕውቀት ብቻ አይደለም ብለን ነው፡፡ እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ይናገ ራል ብለን ነው፡፡ተው ብታውቁበት ይሻላል፡፡ እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆችን ሊያስነሣ ይችላል፡፡ (በዚህ ጊዜ ሰባኪው ትምህርቱን ጨረሰ፡፡ እልል ተባለ ተጨበጨበ)ወይ ግሩም ቀበሌ ክርስትና ተነሥታ እዚህ መጣች፡፡ አሁን ደግሞ ሌላው ይመጣና ከዚያ የቀጠለ ይሁን፣ የበለጠ ይሁን፣ የተለየ ይሁን፣ ያንን የሚያፈርስ ይሁን፣ የሚቃወም ይሁን ደግሞ ያስተምራል፡፡ እንዴው ሥርዓት የሚያወጣ የለም፡፡ ምነው እንደ ቅዳሴው ግፃዌ ቢሠራለት፡፡ የትኛው ከየትኛው እንደሚቀጥል አይታወቅም?
ያም ይመጣና ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ይሄዳል፣ ይሄም ይመጣና ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ይሄዳል፡፡ ሁልጊዜ ተስፋ እንድንቆርጥ፣ እግዚአብሔር ቀጭ፣መዓት አምጭ፣ ተቆጭ፣ ብቻ ነው እንዴ? መሐሪስ አይደለም፣ ይቅር ባይስ አይደለም፣ ተስፋ ሰጭስ አይደለም፡፡ አንዳንዴኮ የሰባክያን እግዚአብሔር የተለየ እግዚአብሔር ሳይሆን አይቀርም፡፡ እናንተን ዝም ብሎ እኛን ብቻ የሚቀጣበት ምክንያት ምንድን ነው?ችግሩኮ አንደኛው ሰባኪ ሌላው ሲያስተምር አይሰማም፡፡ ሊጨርስ ሲል ይመጣና የተለየ መስሎት ያንኑ ደግሞ ያስተምረናል፤ የባሰው ደግሞ የሚቃወም ነገር ይነግረናል፡፡ እኛም ለሁሉም እናጨበጭባለን፡፡
(ሰባኪው ስለ ራሱ መናገር ሲጀምር) በል ስለ እግዚአብሔር የምትነግረን መስሎኝ ነበር እንጂ ስላንተማ ብዙ ዐውቅ የለ ብለው ምእመኑ ልባቸውን ዘጉ፡፡
(አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትምህርት ይሰጣል፡፡ እኒህ ምእመን ቁጭ ብለው ይሰማሉ፡፡ የሰባኪው ሁኔታ አልጣማቸውምና በልባቸው እንዲህ ያማርራሉ፡፡)
«ምን ገባችሁ ገባችሁ ይላል፤ ይልቅ እንዲገባን አድርጎ አያስተምረንም፡፡ አሁን ኢየሱስ ከናዝሬት ወደ ገሊላ ሄደ ብሎ እልል በሉ ማለት ምን ማለት ነው፡፡ አሁን እኛ እልል የምንለው ገሊላ ስለ ሄደ ነው፤ ከናዝሬት ስለተነሣ ነው? ወይስ ስለሄደ ነው? እና ላይሄድ ኖሯል፡፡ ለምን ሄደ? እንዴት ሄደ? ሄዶ ምን አገኘን እያለ እንዲነግረን እንጂ ወደ ገሊላ መሄድማ እማሆይ አማረችስ ባለፈው ጊዜ ኢዬሩሳሌምን ሲሳለሙ ገሊላ ሄደው አልነበረም? ወይ አንተ ፈጣሪ፡፡
ልሂድ ልውረድ ልጄንም ላምጣው፣ እያሉ በርእስ መቀለድ ምን የሚሉት አባዜ ነው፡፡ ሰሞኑንማ የእብራይስጥ ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ፈልጋችሁ ያንን ርእስ ካላደረጋችሁ ትታሠራላችሁ የተባላችሁ ነው የምትመስሉት፡፡
አምሳ ዳቦ ከመላስ አንደ ዳቦ መቅመስ አሉ፡፡ አሁን ይህንን ሁሉ ጥቅስ ከመዘርገፍ አንዱን ትንትን አድርጎ ቢያስተምረን አይሻልም፡፡ ስንት ሕፃናት አሉ፡፡ አረጋውያን አሉ፡፡ መጻፍ የማይችሉ አሉ፡፡ ምን ያደርጉታል አሁን፡፡ «ቀላል አይደለንም» ለማለት ካልሆነ በቀር፡፡እኔ የምለው የስብከት ዓላማው ማስተማር መሆኑ ቀርቶ ማዝናናት ሆነ እንዴ፡፡ እነ ክበበው ገዳ ምን ሠርተው ሊበሉ ነው እንዲህ አገልጋዩ ሁሉ ቀልደኛ ከሆነ፡፡ ቅዳሴ ቢያልቅበት ቀረርቶ ሞላበት አሉ እማሆይ አማረች፡፡ ቆይ አሁን ምን አድርጉ ነው የሚሉን? ኑ ተባልን መጣን፤ አዋጡ ተባልን አዋጣን፤ ጹሙ ተባልን ጾምን፣ ጸልዩ ተባልን ጸለይን፣ ገዳም ሂዱ ተባልን ደርሰን መጣን፣ መጻፍ ግዙ አሉን ገዛን፣ ካሴት ግዙ አሉን ገዛን፣ እልል በሉ ተባልን አልን፣ አጨብጭቡ ተባልን አጨበጨብን፣ አሁንም ይመጡና ኃጢአታ ችሁ ነው ይህንን ሁሉ መዓት ያመጣው ይሉናል፡፡ እሺ ደግሞ ምን ቀረን?አሁን ማን ይሙት ችግር ያለው ከኛ ነው ከእናንተ፡፡ የጥንት ሰዎች ዕድለኞች ሳይሆኑ አልቀሩም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሄደው ገድል እና ተአምር ሰምተው ነበር የሚመጡት፡፡ እኛ በናንተ ምክንያት ጭቅጭቅ እና ንትርክ ሆነኮ የምንሰማው፡፡ ስለ ጊዮርጊስ እና ተክለ ሃይማኖት፣ ስለ ጳውሎስ እና ጴጥሮስ፣ ስለ ክርስቶስ ሠምራ እና መስቀል ክብራ መስማት ትተን ስለ ሰባኪ እገሌ እና ሰባኪ እገሌ፣ ስለ እገሌ ቡድን እና እገሌ ቡድን ሆነኮ የምንሰማው፡፡ አይ ስምንተኛው ሺ፡፡
ስምንተኛው ሺ ቢሆን ነው እንጂ የማይጾሙ የሚጾሙትን፣ የማያስቀድሱ የሚያስቀድሱትን፣ የማይፋቀሩ የሚፋቀሩትን፣ ያልጸኑት የጸኑትን፣ የማይቆርቡ የሚቆርቡትን፣ ዓለምን ያልተው ዓለምን የተውትን፣ ያላመኑ ያመኑትን የሚያስተምሩት፤ ሌላ ምን ቢሆን ነው?
አሁን የት እንሂድ? ከዓለም ወደዚህ መጣን፤ ከዘህ ደግሞ ወዴት እንሂድ፡፡ እንዴው ለመሆኑ ስለ ፓትርያርክ፣ ስለ ጳጳስ፣ ስለ ሲኖዶስ፣ ስለ ካህን፣ ስለ ዲያቆን፣ ስለ ባሕታዊ፣ ስለ መነኩሴ፣ ስለ ሰባኪ ደግ ነገር የምንሰማበት ዘመን ይመጣ ይሆን፡፡ ስለ ገዳማት የምንሰማው ሁሉ ተራቡ፣ ተቸገሩ፣ አበምኔቱ ተማሪዎችን አባረሩ፣ መነኮሳቱ አበ ምኔቱን አባረሩ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው ገድል ተጋድለው ተአምር አደረጉ የሚል የምንሰማው፡፡ስለ ጳጳሳት የምንሰማው በራቸው ተደበደበ፣ በሑዳዴ ጾም ከበሮ አስመቱ፣ በሰው ሀገረ ስብከት ገብተው አተራመሱ፣ ቤት ገዙ፣ መኪና ገዙ፣ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው እንደነ ዮሐንስ አፈወርቅ ለእውነት ተጋደሉ የሚል ወሬ የምንሰማው፡፡ ስለ ፓትርያርክ የምንሰማው እገሊት ትመራቸዋለች፣ ሐውልት ሠሩ፣ ውጭ ሀገር ሄደው ተዝናኑ፣ ገንዘብ አባከኑ፣ በዘመድ ሠሩ፣ የሚል ሆነ፡፡ መቼ ነው እንደ አትናቴዎስ ለሃይማ ኖታቸው መሥዋዕትነት ከፈሉ፣ እንደ ድሜጥሮስ ተአምር አደረጉ የሚል የምንሰማው፡፡ አልታደልንም መሰል፡፡የጥንት ሰዎች በየ ደብሩ ሊቃውንቱ ምሥጢር እና ቅኔ ሲዘርፉ ነበር አልነበር እንዴ ያሉን፡፡ ምነው በኛ ዘመን ቅኔው ቀርቶ ሙዳየ ምጽዋት ብቻ ሆነ የሚዘረፈው፡፡ በየትምህርቱ ስንሰማ ታሥረው በግንድ፣ ተይዘው በግድ ተሾሙ አይደል እንዴ የምትሉን፡፡ ይኼ የነገራችሁን ነገር ተረት ቢሆን ነው እንጂ እንዴት በኛ ዘመን ሊለወጥ ቻለ ታድያ፡፡አንዳንዴኮ እዚያው ተአምረ ማርያማችንን ብቻ እየሰማን፣ ከግብጽ በሚመጣ አንድ ጳጳስ እየተባረክን ውስጡን ሳናውቀው በቀረን ኖሮ ያሰኛል፡፡ እንዴው እነዚህ ሐዋርያት የሚባሉ ይህንን መጽሐፍ የጻፉት በምን ቀን ነው? የአባቶቻችን ተረት እንኳን ለዛ ነበረው፡፡ ማቴዎስ እንዲህ አለ፤ ሉቃስ ይህንን አለ፡፡ ጳውሎስ እንዲህ አለ፡፡ እሺ አለ፡፡ ደግሞኮ «አያችሁ» ይለናል፡፡ ምኑን ነው የምናየው፡፡ እግዚአብሔርንማ እንዳናየው አንተው ራስህ ጋርደህን፡፡ ምን አስተማረ? መባሉ ቀርቶ ማን አስተማረ ሆነ፡፡ ስንት ሰው ተለወጠ? መሆኑ ቀርቶ ስንት ሰው ተሰበሰበ ሆነ፡፡ እኛ የዚህን ዓለም የአለባበሰ ፋሽን እንድንተው አስተማራችሁን፡፡ እሺ ብለን ትተን ስንመጣ እናንተ የየቀሚሱን ዓይነት ፋሽን አመጣችሁት፡፡ ምንድን ነው ይኼ ሁሉ አሸንክታብ? እናንተ መድረክ ላይ ገዝፋችሁ እየታያችሁ ጌታን በየት እንየው፡፡ የሚነገረው ስለ እናንተ ነው፡፡ «ጸጋ የበዛለት፣ታዋቂ፣ ልዩ፣ ልብ ሰባሪ፣አጥንት ነቅናቂ» ከበሮ ለምን ይጮኻል ቢሉ ውስጡ ባዶ ስለሆነ ነው አሉ አሉ፡፡ ተግባራችሁ ይነግረናልኮ፣ ብዙ ማስታወቂያ አያስፈልግም፡፡ እናንተ ስለ እግዚአብሔር ተናገሩ፣ እርሱ ስለ እናንተ ይናገራል፡፡ እናንተ ስለ ራሳችሁ ስለምትናገሩ ግን እርሱን ዝም አሰኛችሁት፡፡እንዲያውም ብዙ ሕዝብ ከሌለ አንመጣም ትላላችሁ አሉ፡፡ ለመሆኑ ይኼ እናንተ የያዛችሁት መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ አንዲት ሳምራዊትን ሴት ለብቻዋ ማስተማሩን አይናገርም ይሆን፡፡ ለመሆኑ ስብከት ለእናንተ ሥራ ነው ወይስ አገልግሎት? ይህንን ሕዝብ ምን እናቅርብለት ብላችሁ ትጨነቃላችሁ? ትጸልያላችሁ፣ ታነባላችሁ? ትጠይቃላችሁ? ወይስ? ምናልባት የማትኖሩበትን ስለምታስ ተምሩን ይሆን መለወጥ ያቃተን? የሌላችሁን ስለምትለግሱን ይሆን ብዛት እንጂ ጥራት ሊኖረን ያልቻለው? ክርስቲያን ታደርጉናላችሁ ብለን ብንመጣ ቲፎዞ አደረጋችሁን፡፡ ለቲፎዞ ለቲፎዞማ አርሴናልና ማንቸስተር ነበሩልንኮ፡፡ ሲገባባቸው ተናደን ሲያገቡ ጨፍረን ቤታችን እንገባ ነበር፡፡ አሁንምኮ እንደዚያ አደረጋችሁት ሁሉም ቲፎዞ ሰብሳቢ ሆነ፡፡ የእገሌ ተከታይ ይባልልኛል፡፡ አስከትላችሁ አስከትላችሁ የት ታደርሱን ይሆን?የታደሉት የዮሐንስ መጥምቅ ተከታዮች መጨረሻቸው ከክርስቶስ ጋር መገናኘት ሆነ፡፡ እኔ ዝቅ ዝቅ ልል እርሱ ግን ከፍ ከፍ ሊል ይገባዋል ብሎ አገናኛቸው፡፡ የርሱ ሥራ ድልድይ መሆን ነበረ፡፡ እኛ የናንተ ተከታዮችስ ታገናኙን ይሆን? ቆይ ግን የሚያስፈልገንን ነው የምትነግሩን ወይስ የምትፈልጉትን? ልታሳውቁን ነው የምትመጡት ወይስ ማወቃችሁን ልትነግሩን፡፡ የምታስተምሩትንስ ታውቁታላችሁ ወይስ ታምኑበታላችሁ?
ቢቻል የምትታዩ ከዋክብት ሁኑልን፣ ባይቻል ደግሞ የማትታዩ ከዋክብት ሁኑ፡፡ ቢቻል አርአያችሁን ምሳሌያችሁን እንድንከተል የምትነግሩንን ብትኖሩት፣ የምታስተምሩትን በእናንተ ብናየው፤ ባይቻል ደግሞ የማታስተምሩንን በእናንተ እንዳናየው ብታደርጉ፡፡
እንዴው ግን እዚህ መሬት ስንቀመጥ የማናውቅ እንመስላችኋለን? እዚህ ቦታኮ በእድሜም በዕውቀትም የምንበልጣችሁ ሰዎች አለን፡፡ አጋጣሚውኮ ነው እናንተን ለመድረክ እኛን ለአግዳሚ ወንበር የዳረገን፡፡ ምናልባትም አንዳንዶቻችን በትኅትና ምክንያት እንጂ ርእሱን ስትናገሩ እንደ ነጣቂ ባለ ቅኔ መደምደሚያችሁንም እናውቀዋለንኮ፡፡ እኛኮ እየተማርን ያለነው ቃለ እግዚአብሔር ምግብ ስለሆነ ነው፡፡ ቃለ እግዚአብሔርኮ ዕውቀት ብቻ አይደለም ብለን ነው፡፡ እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ይናገ ራል ብለን ነው፡፡ተው ብታውቁበት ይሻላል፡፡ እግዚአብሔር ከእነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆችን ሊያስነሣ ይችላል፡፡ (በዚህ ጊዜ ሰባኪው ትምህርቱን ጨረሰ፡፡ እልል ተባለ ተጨበጨበ)ወይ ግሩም ቀበሌ ክርስትና ተነሥታ እዚህ መጣች፡፡ አሁን ደግሞ ሌላው ይመጣና ከዚያ የቀጠለ ይሁን፣ የበለጠ ይሁን፣ የተለየ ይሁን፣ ያንን የሚያፈርስ ይሁን፣ የሚቃወም ይሁን ደግሞ ያስተምራል፡፡ እንዴው ሥርዓት የሚያወጣ የለም፡፡ ምነው እንደ ቅዳሴው ግፃዌ ቢሠራለት፡፡ የትኛው ከየትኛው እንደሚቀጥል አይታወቅም?
ያም ይመጣና ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ይሄዳል፣ ይሄም ይመጣና ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ጨፍጭፎን ይሄዳል፡፡ ሁልጊዜ ተስፋ እንድንቆርጥ፣ እግዚአብሔር ቀጭ፣መዓት አምጭ፣ ተቆጭ፣ ብቻ ነው እንዴ? መሐሪስ አይደለም፣ ይቅር ባይስ አይደለም፣ ተስፋ ሰጭስ አይደለም፡፡ አንዳንዴኮ የሰባክያን እግዚአብሔር የተለየ እግዚአብሔር ሳይሆን አይቀርም፡፡ እናንተን ዝም ብሎ እኛን ብቻ የሚቀጣበት ምክንያት ምንድን ነው?ችግሩኮ አንደኛው ሰባኪ ሌላው ሲያስተምር አይሰማም፡፡ ሊጨርስ ሲል ይመጣና የተለየ መስሎት ያንኑ ደግሞ ያስተምረናል፤ የባሰው ደግሞ የሚቃወም ነገር ይነግረናል፡፡ እኛም ለሁሉም እናጨበጭባለን፡፡
(ሰባኪው ስለ ራሱ መናገር ሲጀምር) በል ስለ እግዚአብሔር የምትነግረን መስሎኝ ነበር እንጂ ስላንተማ ብዙ ዐውቅ የለ ብለው ምእመኑ ልባቸውን ዘጉ፡፡
Monday, January 2, 2012
የገና በዓል አከባበር በዙሪክ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አርብ ታኅሳስ 27 ቀን በ 1900 ሰዓት ይጀምራል!
የጌታችንና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የ2004 የልደት በዓል (ገና)በዙሪክ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መርሃግብር ዓርብ ታኅሳስ 27 ቀን (6.1.2012) በ1900 ሰዓት ይጀምራል::በዓሉን በደመቀ ሁኔታ ለማክበር ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል::
ቀደም ሲል ቀኑንና ሰዓቱን በሚመለከት ተነግሮ የነበረው በዚህ መስተካከሉን በትሕትና እናስታውቃለን:: ላልሰሙ ወገኖች እንድታሰሙ በጌታችንና በመደሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አደራ እንላለን::
በዙሪክ የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም የሰበካ ጉባኤ
ቀደም ሲል ቀኑንና ሰዓቱን በሚመለከት ተነግሮ የነበረው በዚህ መስተካከሉን በትሕትና እናስታውቃለን:: ላልሰሙ ወገኖች እንድታሰሙ በጌታችንና በመደሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አደራ እንላለን::
በዙሪክ የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም የሰበካ ጉባኤ
ስለ ገና በዓል
ስለ ዘንድሮው የገና በዓል ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ የላኩልንን ይመልከቱ;
---------------------------------------
ታኅሣሥ 28 ቀን፥ 2004 ዓ.ም.
እንኳን ለዘመነ ዮሐንስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ልደት የሚከበረው በታኅሣሥ 29፥ በሠግር ዓመት ግን በታኅሣሥ 28 ስለሆነ ዘንድሮ የሚከበረው በታኅሣሥ
28 ቀን ነው።
በሀገራችን የሠግር ዓመት መቼ እንደሆነ የማያውቁ ሰዎች ልደት የሚከበርበት ቀን ይምታታባቸዋል።
አባቶቻችን ለዚህ መፍትሔ ሲፈልጉ ለአራቱ ወንጌላውያን አንድ አንድ ዓመት ሰጥተው ዓመቱን "ዘመነ
ማቴዎስ"፥ "ዘመነ ማርቆስ"፥ "ዘመነ ሉቃስ"፥ "ዘመነ ዮሐንስ" እያሉ ያስኬዱና ዓመቱ እንደ ዘንድሮው
ዘመነ ዮሐንስ ሲሆን ልደት የሚውለው በታኅሣሥ 28 ነው ይሉናል--በአራት ዓመት ወይም በየአራት ዓመቱ
አንዴ ማለታቸው ነው።
ዓመቱ ለምን "ሠግር" ተባለ? "ሠገረ" ፥ "ተሻገረ" የሚሉት የአማርኛ ቃላት "ሠግር" ከሚለው የግዕዝ ቃል
ጋር ዝምድና አላቸው። "ሠግር" ማለት "ተሻጋሪ"፥ "ዘላይ" ማለት ነው። ዓመቱ 365 ቀናት መሆኑ ቀርቶ
366 ቀን ሲሆን ምዕራባውያን "Leap Year" ይሉታል፤ ያው "ዘላይ ዓመት" ማለታቸው ነው። በእኛ
የአቈጣጠር ዘዴ ጳጒሜ 5 ቀናት መሆኗ ቀርቶ 6 ቀን ስትሆን ማለት ነው። ቈጠራው የሚምታታው
"የሠግር ዓመት" የሚባለው ዘመነ ሉቃስ ነው ወይስ ዘመነ ዮሐንስ ከሚለው ጥያቄ ላይ ነው። ምክንያቱም
ጳጒሜ 6 ቀናት የምትሆነው በዘመነ ሉቃስ ነው። ልደት በታኅሣሥ 28 የሚውለው ግን በዘመነ ዮሐንስ
ንው።
እኛ ያየነው ጳጒሜ በዘመነ ሉቃስ 6 ቀናት ስትሆን ዘመነ ዮሐንስ የሚጀምርበትን፥ መስከረም 1ን፥
በአንድ ቀን ማስዘግየቷን ነው። አንድ ቀን ታስዘልለውና እንደሌሎቹ ዓመታት በ1 መጀመሩን ትቶ፥ 2
ሊሆን በሚገባው ቀን ይጀምራል። በአዘቦት ዓመታት መስከረም 2 ሊሆን የሚገባውን ቀን መስከረም 1
አለው ማለት ነው። መስከረም አንድ በአንድ ቀን ዘግይቶ ከጀመረ ("ከጀመረ" በማለት ፈንታ "ከባተ"
ይላሉ)፥ ወራቱ ሁሉ (ታኅሣሥን ጨምሮ ማለት ነው) አንድ ቀን እያሳለፉ መጀመር (መባት) ግድ
ይሆንባቸዋል። ልደት አብሮ አይዘገይም፤ ቦታውን እንደያዘ ይኖራል። ስለዚህ በሠግር ዓመት ታኅሣሥ
አንድ ቀን ዘግይቶ እ2 ላይ ከጀመረ ልደት የሚውልበት ታኅሣሥ 29 ቀደም ብሎ በታኅሣሥ 28 ቀን
ይውላል። የሠግር 28 ቀንና የአዘቦቱ 29 ቀን ሁለቱም እኩል ዮናርዮስ 7 (January 7) ናቸው።
ልደትን የምታከብሩ ሁሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም ያደረሳችሁ።
ጌታቸው ኃይሌ።
---------------------------------------
ታኅሣሥ 28 ቀን፥ 2004 ዓ.ም.
እንኳን ለዘመነ ዮሐንስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ልደት የሚከበረው በታኅሣሥ 29፥ በሠግር ዓመት ግን በታኅሣሥ 28 ስለሆነ ዘንድሮ የሚከበረው በታኅሣሥ
28 ቀን ነው።
በሀገራችን የሠግር ዓመት መቼ እንደሆነ የማያውቁ ሰዎች ልደት የሚከበርበት ቀን ይምታታባቸዋል።
አባቶቻችን ለዚህ መፍትሔ ሲፈልጉ ለአራቱ ወንጌላውያን አንድ አንድ ዓመት ሰጥተው ዓመቱን "ዘመነ
ማቴዎስ"፥ "ዘመነ ማርቆስ"፥ "ዘመነ ሉቃስ"፥ "ዘመነ ዮሐንስ" እያሉ ያስኬዱና ዓመቱ እንደ ዘንድሮው
ዘመነ ዮሐንስ ሲሆን ልደት የሚውለው በታኅሣሥ 28 ነው ይሉናል--በአራት ዓመት ወይም በየአራት ዓመቱ
አንዴ ማለታቸው ነው።
ዓመቱ ለምን "ሠግር" ተባለ? "ሠገረ" ፥ "ተሻገረ" የሚሉት የአማርኛ ቃላት "ሠግር" ከሚለው የግዕዝ ቃል
ጋር ዝምድና አላቸው። "ሠግር" ማለት "ተሻጋሪ"፥ "ዘላይ" ማለት ነው። ዓመቱ 365 ቀናት መሆኑ ቀርቶ
366 ቀን ሲሆን ምዕራባውያን "Leap Year" ይሉታል፤ ያው "ዘላይ ዓመት" ማለታቸው ነው። በእኛ
የአቈጣጠር ዘዴ ጳጒሜ 5 ቀናት መሆኗ ቀርቶ 6 ቀን ስትሆን ማለት ነው። ቈጠራው የሚምታታው
"የሠግር ዓመት" የሚባለው ዘመነ ሉቃስ ነው ወይስ ዘመነ ዮሐንስ ከሚለው ጥያቄ ላይ ነው። ምክንያቱም
ጳጒሜ 6 ቀናት የምትሆነው በዘመነ ሉቃስ ነው። ልደት በታኅሣሥ 28 የሚውለው ግን በዘመነ ዮሐንስ
ንው።
እኛ ያየነው ጳጒሜ በዘመነ ሉቃስ 6 ቀናት ስትሆን ዘመነ ዮሐንስ የሚጀምርበትን፥ መስከረም 1ን፥
በአንድ ቀን ማስዘግየቷን ነው። አንድ ቀን ታስዘልለውና እንደሌሎቹ ዓመታት በ1 መጀመሩን ትቶ፥ 2
ሊሆን በሚገባው ቀን ይጀምራል። በአዘቦት ዓመታት መስከረም 2 ሊሆን የሚገባውን ቀን መስከረም 1
አለው ማለት ነው። መስከረም አንድ በአንድ ቀን ዘግይቶ ከጀመረ ("ከጀመረ" በማለት ፈንታ "ከባተ"
ይላሉ)፥ ወራቱ ሁሉ (ታኅሣሥን ጨምሮ ማለት ነው) አንድ ቀን እያሳለፉ መጀመር (መባት) ግድ
ይሆንባቸዋል። ልደት አብሮ አይዘገይም፤ ቦታውን እንደያዘ ይኖራል። ስለዚህ በሠግር ዓመት ታኅሣሥ
አንድ ቀን ዘግይቶ እ2 ላይ ከጀመረ ልደት የሚውልበት ታኅሣሥ 29 ቀደም ብሎ በታኅሣሥ 28 ቀን
ይውላል። የሠግር 28 ቀንና የአዘቦቱ 29 ቀን ሁለቱም እኩል ዮናርዮስ 7 (January 7) ናቸው።
ልደትን የምታከብሩ ሁሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም ያደረሳችሁ።
ጌታቸው ኃይሌ።
Saturday, May 21, 2011
ማስታወቅያ!
በበርን የዳድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሐይማኖትን ዓመታዊ ንግስ ምክንያት በማድረግ የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን በጋራ ጉዞ ግንቦት 14, 2003 (22.05.2011) እንሄዳለን:: ስለሆነም ቤተ ክርስቲያኑቱ የተለመደ መርሃ ግብሯ በዚህ ዕለት አይኖርም:: የሚቀጥለው ሳምንት ዕሑድ ግንቦት 21, 2003 (29.05.2011) በዕለተ ማርያም ቅዳሴ የሚኖር መሆኑን በትሕትና እናስታውቃለን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር
የሰበካ ጉባዔው
በበርን የዳድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሐይማኖትን ዓመታዊ ንግስ ምክንያት በማድረግ የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን በጋራ ጉዞ ግንቦት 14, 2003 (22.05.2011) እንሄዳለን:: ስለሆነም ቤተ ክርስቲያኑቱ የተለመደ መርሃ ግብሯ በዚህ ዕለት አይኖርም:: የሚቀጥለው ሳምንት ዕሑድ ግንቦት 21, 2003 (29.05.2011) በዕለተ ማርያም ቅዳሴ የሚኖር መሆኑን በትሕትና እናስታውቃለን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር
የሰበካ ጉባዔው
Friday, June 25, 2010
Abune Melketsedek verstorben
Seine Heiligkeit Abune Melketsedek, Erzbischof von Kembata, Hadiya, Gurage und Silte ist letzten Samstag verstorben.
Unter seiner Heiligkeit fand das tausendjährige Mehur Eyesus Kloster zu neuem Glanze. Er liess es ausbauen und um Bildungseinrichtungen erweitern. Zudem reiste er häufig durch Europa, um Spenden für seine unzähligen humanitären und geistlichen Projekte zu sammeln.So kam seine Heiligkeit auch mehrmals in die Schweiz und nahm auch zweimal an der Orthodoxen Vesper zu Ehren der Stadtheiligen Felix, Regula und Exuperantius in Zürich teil.
Unermüdlich setzte er sich für Waisenkinder ein, denen er ein neues Zuhause gab und ihnen eine Schulbildung ermöglichte.
Die Debre Gennet Qiddist Maryam Kirchgemeinde in Opfikon-Glattbrugg wurde von seiner Heiligkeit mehrmals mit einem Besuch beehrt, wodurch über die Jahre eine enge Verbindung zu ihm entstanden ist.
Videos:
Seine Heiligkeit besucht das St. Avgin Kloster der syrisch-orthodoxen Kirche:
Seine Heiligkeit an der Orthodoxen Vesper zu Ehren der Zürcher Stadtheiligen:
መለያ ቃላት:
Bischof,
Erzbischof,
Eyesus,
Kirche,
Kloster,
Mehur,
Melketsedek,
orthodox,
Verstorben,
Vesper,
Waisenkinder,
äthiopisch
| አቀባበል: |
Sunday, May 9, 2010
በእሾሆች መካከል ያበበች በእውነት የሃይማኖት አበባ ናት
በማዕከለ አስዋክ ዘፀገየት ፅጌ ሃይማኖት ዘበአማን፤
በእሾሆች መካከል ያበበች በእውነት የሃይማኖት አበባ ናት፤
ቅዱስ ያሬድ፤
ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር በኃጢአት ለወደቀው አዳም የገባለት ቃል ኪዳን « ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ» የሚል እንደነበር ሁሉ ለታላቁ የሃይማኖት አባት አብርሃምም እንደዚሁ «በዘርህ አህዛብ ይበረካሉ» የሚል ቃልኪዳን ገብቶለት ነበር ዘፍ፤12፤2-3 የሐ.ስራ 3፤25 የሰጠውን ቃል ኪዳን የማያስቀር አምላክ ጊዜው ሲደርስ ፈፀመው። መቼም ፍጥረት ያለ ታሪክ ታሪክም ያለፍጥረት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፤ ስለዚህ በደግነትም ሆነ በክፋት ብዙም ሆነ ጥቂት ታሪክ የሌለው ፍጥረት የለም። ይህንን ለማለት የተፈለገው በንፅህናዋ ያለተጓዳኝ ተፈጥራ ብቻዋን የኖረች የወላደተ አምላክ ልደት እንደ እርሷ ክብር ሳይሆን በመጠኑ ለማስታወስ ተፈልጐ ነው።
ምክንያቱም ከድንግል ማርያም በቀር ማንኛውም ፍጥረት ያለ ተጓዳኝ ተፈጥሮ የኖረ የለም ያልተፈጠረው አንድ አምላክ ብቻ እንጂ፡፡ ድንግልናዋም ቢሆን ከመነገር በላይ ነው፤¸በድንግልና ፀንሶ በድንግልና ወልዶ ድንግል ሆኖ የኖረ ፍጥረት ስለማይገኝ በዚህም ብቸኛ ናት።
እንዲህ ያለችውን ያስገኙ ወላጆቿ ኢያቄምና ሐናም በጥንተ ተፈጥሮ አንድ ወንድ በአንድ ሴት በሚለው ንፁህ ጋብቻ የኖሩ፤ በእግዚአብሔር ሕግ የሚመሩ፤ በኅብረተሰባቸው ዘንድ የተከበሩ ፃድቃን እንደነበሩ በስነ ምግባር የታነፀ የሕይወት ታሪካቸው ይናገራል።
ይህን በመሰለ የህይወት ኑሮ እየኖሩ ፅድቅ የማይጠይቅ፤ ማንም ያላጣውንና ከከበረ ጋብቻቸው ማግኘት የሚገባቸውን ልጅ ሳያገኙ ብዙ ዘመናትን አሳልፈዋል። ቢሆንም ትዳራቸው እግዚአብሔር ያልተለየው በእግዚአብሔር የሚጠበቅ ሰላማዊ ነበር። እነሱም ቢሆኑ ዝም ብለው አልተቀመጡም ወደ ሚመለከተው ክፍል በንፁሕ መስዋዕትና ፀሎት መላልሰው ሲያመለክቱ ኖረዋል። በትክክል የለመኑትን የማይነሳ በእውነት የነገሩትን የማይረሳ አምላክ ከእነሱ በላይ ለእነሱ በማሰብ ትዳራቸውን ለትልቅ ነገር ሲጠብቀው ኖሮ በጊዜው ጊዜ የማንም ጋብቻ ሊያስገኛት ያልቻለውና የማይችልው የከበረች ልጅ አስረክቧቸዋል።
በመሆኑም በመዝሙረ ዳዊት « በጨነቀኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት ወደ አምላኬም ጮህኹ ከመቅድሱም ቃሌን ሰማኝ፤» መዝ፤17፤6 እንደተባለው ልዑል እግዚአብሔር የቅዱስ ኢያቄምና የቅድስት ሐናን ፀሎትና ልመናቸውን ተቀብሎ ለማደሪያነት የመረጣት ወላዲተ አምላክ ነሐሴ 7 ቀን ተፀንሳለች። በተፀነሰችም ጊዜ ብዙ ተዓምራት ተደርገዋል በነቢያት ዘመን ነቢዩ ኤልያስ ( 2ኛ ፤ነገ.13፤2) በዘመነ ሐዋርያት እነ ቅዱስ ጴጥሮስ የሐዋ. ሥራ 5፤15 በጥላቸው ገቢረ ተዓምራት እንደፈጸሙ ሁሉ እመቤታችንም በማህፀነ ሐና እያለች የቤርሳቤህን ዓይን አብርታለች።
የፅንሱም ወራት ከተፈጸመ በኋላ ግንቦት 1 ቀን ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ ደምግባትና መወደድ ያላት ወላዲት አምላክ ተወለደች። « ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ ሰማዮሙኒ አስረቀት ፀሐየ» ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱ ሰማይም ፀሐይን አስገኘች(ወለደች) እንደለ ሊቁ።
እመቤታችን የተወለደችው ሊባኖስ በተባለ ተራራ ላይ ነው። በሊባኖስ ተራራ ላይ እመቤታችን እንድትወለድ ምክንያቶቹ አይሁድ ቢሆኑም ምሥጢሩ ግን የተነገረው ትንቢት እንዲፈጸም ነው።
ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ መኃ 4፤8
ሙሽሪት ሆይ ከሊባኖስ ነይ ከሊባኖስ ነይ የሚል ትንቢት ነበርና። በዚህ እለትም የመላው ዓለም የጨለማ ህይወት በብርሃን፤ ዓመተ ፍዳ ዓመት ኩነኔ በዓመተ ምህረት የሚለወጥበት ዋዜማ በመሆኑ ታላቅ ደስታ ተደርገ። ከዲያብሎስና ሠራዊቱ በስተቀር ዓለም የመልካም ዜና መጀመርያውን ቀን ሲያውቀውም ሳያውቀውም አከበረ የአምላክ እናት ተወልዳለችና።
እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማንያን የድንግል ማርያም የአሥራት ልጆች እንደመሆናችን መጠን እናታችን ቅድስት ማርያም ቤተሰቦቿ ከቤታቸው እና ከቄያቸው ተሰደው ብዙ አፀድ ባለበት በአድባረ ሊባኖስ በመወለዷ ይህንን የልደቷን ቀን በገጠር በከተማ፤ ልጅ አዋቂው፤ ሀብታምና ድሀው በአንድነት በሰፈር ውስጥ በመሰባሰብ ሁሉም ያለውን በማምጣት በጋራ በፍቅር በደስታ ያከብራሉ፤ ምንም እንኳ አንዳንዶች ይህንን ያማረ ትውፊት ለባዕድ አምልኮት ቢጠቀሙበትም ከእንዲህ ያለ ምግባረ ብልሹነት ተቆጥበን የመጀመርያውን ዓላማ ጠብቀን የዚህችን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት ቅድስት እናት በዓለ ልደት የእያንዳችን የድህነት ብስራት ቀን መሆኑን አውቀን ያለምንም ልዩነት በአንድነት፤በሰላም፤በፍቅር፤በደስታ ልናከብረውና ሃይማኖታዊ እሴቱ ሳይበላሽ፤ሳይበረዝና ሳይለቅ ለትውልድ ልናስተላልፍ ይገባል።
ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ረድኤት ይርዳን አሜን።
መልአከ ገነት
አባ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ማርያም(ቆሞስ)
ግንቦት 1 ቀን 2002 ዓ/ም
+ + +
የዕለቱ ምስባክ
መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን
ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን
እምኩሉ ተዐይኒሁ ለያዕቆብ
መዝ፣86፣1-2
+ + +
Subscribe to:
Posts (Atom)
