ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Tuesday, May 8, 2012

"ሁሉም በልተው ጠገቡ:የተረፈውም ቁርስራሽ አስራ ሁለት መሶብ ሙሉ አነሱ::" ማቴዎስ 14:20






የግንቦት ልደታ ንግስ በጨረፍታ

የግንቦት ልደታ አከባበር - ከምስል ማሕደራችን

ዕሑድ ሚያዝያ 28 ቀን በዙሪክ/ኦፕፊኮን የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተከናወነውን የንግሥ ሥነ-ሥርዓትና በስተመጨረሻም "አድባር" በቤተ ክርስቲያኑ መናፈሻ ቦታ ላይ እንዴት እንደተከበረ በመጠኑም ቢሆን አመላካች የሆኑ ምስሎች እዚህ ላይ ተለጥፈዋል::




Monday, May 7, 2012

የልደታ በዓል እጅግ ደማቅ በሆነ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ!

የእመቤታችን የድንግል ማርያም የልደት በዓል (ግንቦት ልደታ) እሁድ  ሚያዝያ 28 ቀን 2004 ዓ.ም. በዙሪክ የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀትና ንግሥ ተከበረ:: ክተለያዩ የስዊስ ካንቶኖችና አጎራባች አገሮች በተሰበሰቡ     ምእመናን በተዋሕዷዊ መዝሙሮችና ያሬዳዊ ወረቦች ያማረውን አከባበር  የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በዚህ ገጽ ላይ ይቀርባል::
"ከሺ ቃላት አንድ ምስል በይበልጥ ይገልጻል " ነውና  ምስሎችን ይመልከቱ::
(ፎቶዎች በተስፉ ወልደ ሥላሴ)





Thursday, May 3, 2012

የግንቦት ልደታ የንግሥ ሥነ-ሥርዓት በኦፕፊኮን ደብረ ገነት ቅ.ማርያም ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል!

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

በዙሪክ/ኦፕፊኮን (ስዊዘርላንድ)የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የዘንድሮውን የግንቦት ልደታን የምታከብረው ዕሑድ ሚያዝያ 28 ቀን 2004 ዓ.ም.(06.05.2012) ነው::

እንደተለመደው ሁሉ ለበዓሉ ተስማሚ በሆኑ ያሬዳዊ ዜማዎች: ቅዳሴና ንግሥ የሚከበር ሲሆን ከቅዳሴ በኋላ የእመቤታችንን ልደት ለማስታወስ ጸበል ጸዲቅ ለየት ባለ መልኩ መናፈሻ ውስጥ የሚደረግ መሆኑን የመስተንግዶ ክፍሉ አስታውቋል::

በስዊዘርላንድና አካባቢው ነዋሪ የሆኑ የተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ በዚህ እለተ ሰንበት በመገኝት የበረከቱ ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱ ጥሪዋን ታቀርባለች::