ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Friday, March 23, 2012

ቅዳሴና ትምሕርት በመምሕር ጥበበ ሥላሴ (ከ UK)

ዕሑድ መጋቢት 16 ቀን (25.03.2012) በዙሪክ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴና የስብከተ ወንጌል ትምሕርት የሚኖር መሆኑን የሰበካ ጉባኤው በትሕትና ያስታውቃል:: ቀሲስ (መምሕር) ጥበበ ሥላሴ ከ ታላቋ ብሪታንያ ይመጣሉ::
ምዕመናን ላልሰሙ እያሰማችሁ ሁላችንም የበረከቱ ተሳታፊዎች እንሆን ዘንድ የቸሩ መድሃኔዓለም እርዳታ:የእመቤታችን የድንግል ማርያም ልመናና ጸሎት ከሁላችን ጋር ይሁን!

Wednesday, March 14, 2012

ሰኞ መጋቢት 10 ቀን (19.3.12)የኢትዮጵያ ምሽት በዙሪክ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ ይከበራል!

ሰኞ መጋቢት 10 ቀን (19.03.2012)በዙሪክ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ (Stadthaus Zürich
Stadthausquai 17, 8001 Zürich, Switzerland) "የኢትዮጵያ ምሽት" ይከበራል::
በዝግጅቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የዙሪክ መንግሥት ባለሥልጣናትም ጭምር ይገኛሉ:: በዚሁ የኢትዮጵያን ባሕልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ትስስር ለማሳየት በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ባላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትና ምርምር የሚታወቁት ታዋቂው የ ቴሌቬዥን ጋዜጠኛ ዋልተር ኤገንበርገርና በስዊዘርላንድ የኦርቶዶክሳውያን ማሕበር ዋና ጸሐፊ ያሬድ ሃይለ ሥላሴ ስለኢትዮጵያና የተዋሕዶ እምነት በኢትዮጵያና በዲያስፖራ የሚያሳይ የፊልም ቅንብርና ገለጻ ይቀርባል::

በዚሁ ከ19:00 ጀምሮ በሚከናወነው ዝግጅት ላይ እንድትገኙ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል::
አስታውሱ!
ቦታው:- ዙሪክ ማዘጋጃ ቤት
ቀን:- 19.03.2012
ሰዓት:- 19:00