ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Tuesday, March 2, 2010

ጾም ማለት የምግብ ለውጥ ማድረግ ብቻ ነውን?

በዚህ በጀመርነው የአቢይ ጾም ወቅት ለጿሚው አዳጋች የሚባለው "የጾም ምግብ" በቀላሉ አለማግኘት ነው ይባላል:: ብዙዎች አሣም ደም አለውና አይበላም ይላሉ:: የጾሙ ከፍስኩ እንዳይነካካ ብርቱ ጥንቃቄ የሚያደርጉም ጿሚዎች ቁጥር የሚናቅ አይደለም:: በዚህ በስደት ዓለሙም ቢሆን በተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ከተደነገጉት ሰባቱ አጽዋማት መካከል የአቢይ / ሁዳዴ ጾምን አብዛኛዎቹ አማንያን ይጾሙታል:: የምግብ ለውጥ ይደረጋል ማለት ነው::
ምንም እንኳን ቀን እየተቆጠረ ዛሬ ጾም ስለሆነ ልጠንቀቅ ነገ እፈስካለሁ የሚባል ባይሆንም በተለይ በዚህ ወቅት ልንጾማቸው (ልንታቀብ) የሚገባን ሌሎች ነገሮች ያሉ አይመስሏችሁም?

ሀሜት - ምቀኝነት -ቅናት -ተንኮል -ሸር - ሃሰተኝነት.ወዘተ ከሥጋውና ከቅቤው የበለጠ አያረክሱም? በእርግጥ የባህርይ ለውጥን የሚጠይቅ ቢሆንም ወደ አፍ ከሚገባው ባልተናነሰ ሁኔታ ከአፍ የሚወጣውን መጠንቀቁም ሊዘነጋ የማይገባው የጾም አይነት ይመስለኛል::በዚህ ጉዳይ ላይ በሰፊው እመለስበታለሁ::ጾሙን የሰላም የመፈቃቀር የመተሳሰብና ከእኛ ባነሰ ሁኔታ የሚኖሩትንም የምናስብበት ወቅት ያድርግልን:: ሀገራችን ኢትዮጵያን አምላክ ይጠብቅልን! አሜን::