ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Monday, September 24, 2012

መምሕር ዘበነ ለማ : ዘማሪ ምንዳየ ብርሃኑና ደመራ በደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም (Glattbrugg /Opfikon), Zürich

በሰመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ አሜን::

ዕሑድ መስከረም 20 ቀን 2005 ዓ.ም.(30.09.2012)በደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኦፕፊኮን/ ዙሪክ ከጧቱ አንድ ሰዓት በቅዳሴ ከሚጀምረው መርሃ ግብር ዋና ዋናዎቹን ለመጥቀስ ያህል - በታዋቂው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምሕር ዘበነ ለማ የወንጌል ትምሕርት ተዋዝቶ ከኢትዮጵያ በሚመጣው ዘማሪ ዲያቆን ምንዳዬ ብርሃኑና በዙሪኩ ዘማሪ ጥላሁን አብሽር ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ደምቆ እስከ ደመራው ያደርሰናል:: ደመራው በተለመደው ቦታና ተጋባዥ እንግዶችም በሚገኙበት ኦፕፊኮን / Zunstrasse , 8152 Glattbrugg በታላቅ ሥነ-ሥርዓት እናከብራለን::

የምስራቹን ላልሰሙ ወገኖች አሰምተን በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊዎች እንድንሆን የድብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ጥሪ ታቀርባለች::