ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Monday, April 16, 2012

በዙሪክ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የፋሲካ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ!










በዙሪክ /ኦፕፊኮን የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የዘንድሮው የጌታችንና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በአል እጅግ በጣም ደማቅ በሆነ ሥነ-ሥርአት ተከብሮ ውሏል:: እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስርአት:ከጸሎተ ሓሙስ ጀምሮ የተዘጋጀውን መርሐ ግብር በርካታ ምዕመናን እየተገኙ የበረከቱ ተሳታፊዎች ሆነዋል::
የዘንድሮው የፋሲካ በአል አከባበርን ካለፉት ዓመታት የተለየ ያደረገው ቁጥሩ እጅግ የበዛ ምዕመን መገኘት ብቻ ሳይሆን በትንሳኤው የጸሎት መርሃ ግብር ላይ ክ አምስቱ "ኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት"ተብለው ከሚታወቁት (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀዳሚ ቦታ ካላት)እህት አብያተ ክርስቲያናት መካከል የሕንድና ሶርያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የአውሮጳ ጳጳስ ብጹእ ወዶክተር ሞር አንቲሞስ ማቴዎስ መገኘትና ምዕመናኑን መባረክ ነው::ብጹዕነታቸው ባስተላለፉት መልዕክት ትንሳኤ ለክርስቲያኖች ያለውን ትርጉም ከገለጹ በኋላ ክርስቲያናዊ ሕይወት ለመኖር የሰው ልጆች ቋሚ ጠላት የሆነው ሰይጣንን ጠንክሮ መቋቋምና ድል መንሳትን መቻል ነው ብለዋል::ቀጥለውም ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር ስላለው ታሪካዊና እምነታዊ ትሥስር አስታውሰዋል::በሰሙትና ባዩት መንፈሳዊነትና በተለይም በያሬዳዊ መዝሙራት ከልብ መደሰታቸውን አልሸሸጉም ብጹእነታቸው::

ጸሎተ ቅዳሴውን የመሩት ዶክተር(MD)ወቀሲስ አየለ ከጸሎተ ሐሙስ እስከ እለተ ትንሳኤው በደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ አባላት ትጋትና ይልቁንም በትንሿ ስዊዘርላንድ ውስጥ ከቅርብም ከሩቅም የመጣው ቁጥሩ ይኽን ያህል ይሆናል ብለው ባልጠበቁት ምዕመን ብዛትና ተሳትፎ እንዲሁም ክርስቲያናዊ ቀንአዊነት መደሰታቸውን ና መርካታቸውን ገልጸዋል::




በተመሳሳይ ሁኔታ በጄኔቫ ጸሐዬ ጽድቅ መድሃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የትንሳኤ በአል ከአጎራባች ካንቶኖችና ፈረንሳይም በመጡ በርካታ ምዕመናን አምሮና ደምቆ መከበሩን የሰበካ ጉባኤው አስታውቋል::

No comments:

Post a Comment