ቅድስት ድንግል ማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም
ምስለ ፍቁር ወልዳ

Thursday, May 2, 2013

ፋሲካ በዙሪክ (ኦፕፊኮን) ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን

ሰሞነ ሕማማትን በጋራ ፀሎትና ስግደት ዘወትር ከቀኑ 17  ሰዓት ጀምሮ እያሰብን እንገኛለን፣ 

 ፀሎተ ሐሙስ ከጧቱ አራት ሰዓት (10) ጀምሮ ቅዳሴን ጨምሮ ሙሉ ሥነ ስርዓት ይከናወናል። ዐርብ የጌታችንንና የመድሃኒታችንን  የኢየሱስ ክርስቶስን ሕመሙን፣ ስቅለቱነቱን ለእኛ ሲል በሰዎች እጅ የደረሰበትን መከራ በስግደትና በጸሎት ከጥዋቱ ሶስት (9) ሰዓት ጀምሮ እናስበዋለን።

 ቅዳሜ ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የትንሣኤ በአል በታላቅ ተዋሕዷዊ ሥነ ስርአት የሚከበር መሆኑኑ ለተወደዱ ምዕመናን እያበሰርን ያልሰሙ ወገኖችን አሰምታችሁ የበረከቱ ተሳታፊዎች እንድትሆኑ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እናሳስባለን።

 

No comments:

Post a Comment