ሰኞ መጋቢት 10 ቀን (19.03.2012)በዙሪክ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ (Stadthaus Zürich
Stadthausquai 17, 8001 Zürich, Switzerland) "የኢትዮጵያ ምሽት" ይከበራል::
በዝግጅቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የዙሪክ መንግሥት ባለሥልጣናትም ጭምር ይገኛሉ:: በዚሁ የኢትዮጵያን ባሕልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ትስስር ለማሳየት በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ባላቸው የረጅም ጊዜ ግንኙነትና ምርምር የሚታወቁት ታዋቂው የ ቴሌቬዥን ጋዜጠኛ ዋልተር ኤገንበርገርና በስዊዘርላንድ የኦርቶዶክሳውያን ማሕበር ዋና ጸሐፊ ያሬድ ሃይለ ሥላሴ ስለኢትዮጵያና የተዋሕዶ እምነት በኢትዮጵያና በዲያስፖራ የሚያሳይ የፊልም ቅንብርና ገለጻ ይቀርባል::
በዚሁ ከ19:00 ጀምሮ በሚከናወነው ዝግጅት ላይ እንድትገኙ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል::
አስታውሱ!
ቦታው:- ዙሪክ ማዘጋጃ ቤት
ቀን:- 19.03.2012
ሰዓት:- 19:00
Wednesday, March 14, 2012
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment