በሃገረ ስዊዘርላንድ በአይነቱ የመጀመርያው ነው ተብሎ የታመነው ይኽው ሃይማኖታዊ ጉባኤ የተዘጋጀበት አዳራሽ ከተፈቀደለት 2800 ሰዎች ሶስት እጥፍ በላይ ማስተናገዱ አደገኛ ሊሆን ይችላል ተብሎ ስለታመነና በየሰዓቱ የሕዝቡ ቆጥር አካባቢው ሊያስተናግደው ከሚችለው በላይ አየሆነ በመሄዱ ምኣመኑን ይቅርታ ጠይቆ ተበትኗል::
አዘጋጁ ኮሚቴ በተፈጠረው መጨናነቅ ሃዘኑን እየገለጸ በሌላ በ ኩል ምእመኑ ለመልአከ መንክራት መምሕር ግረማ ያለውንም ክብርና ፍቅር የተገነዘበበት አጋጣሚ በመሆኑ ለቅጣይ ዝግጅቱ ጠቃሚ ልምድ ማግኘቱ ግልጽ ነው:: አንደ ፖሊስ ገለጻ ከሆነ መግባት ክቻሉት ሌላ አካባቢው ከ5000 ባላነሱ ሰዎች ተጥለቅልቆ መዋሉን በአለታዊ ረፖርቱ ዘግቧል::
አዘጋጅ ኮሚቴው በተፈጠረው አሳዛኝ ክስተት ልባዊ ሃዘኑን ለሚመለከታቸው ሁሉ አየገለጸ በቅረቡ በተሻለ ዝግጅት ተወዳጁ መምሕር ግርማን በድጋሚ የጀመሩትን የፈውስ እገልግሎት አንዲቀጥሉ ያቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለዋል:: ስለሆነም ከተገኘው ልምድ ተነስቶ የተሻለና የሕዝቡን ፍላጎት የሚመጥን ዝግጅት ክአሁኑ ለመጀመር ተወስኗል::
በዚህ አጋጣሚ በተፈጠረው አለመመቻቸት አዘጋጅ ኮሚቴው የሚመለከታቸውን ሁሉልባዊ ይቅርታ ይጠይቃል::
No comments:
Post a Comment